አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ለሕብረተሰብ ጥቅም በሚሰሩ የልማት ስራዎች ሁሉም ትብብር ሊያደርግ ይገባል አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት በዛሬው ዕለት በተካሄደው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባ ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ ላይ ነው።
ለማህበረሰብ ጥቅም ከሚሰሩ ልማቶች በተጨማሪ የኢንቨስትመንት የልማት ስራዎች እንደሚከናወኑ ገልጸው፤ እንደ ቴሌ ኮሙኒኬሽን፣ መብራት ኃይል፣ አየር መንገድ፣ የልማት ስራ በሚሰሩበት ወቅት 100 በመቶ ካሳ ይከፍላሉ ብለዋል።
ነገር ግን ካሳ የሚጠየቅበት መንገድ ለምን ዓላማ? የሚለውን በደንብ ማለየት ያስፈልጋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለትምህርት ቤት፣ ሆስፒታል፣ ዩኒቨርሲቲ፣ ለመስራት ሃብት ከተለያዩ ቦታዎች ሲገኝ ለካሳ የሚጠየቀው ገንዘብ ስራውን አስቸጋሪ እንደሚያደርገው ተናግረዋል።
መሰረተ ልማት እንዲሟላ ሲጠየቅ ዋና ተጠቃሚው ማሕበረሰቡ እንደሆነ በመገንዘብ መሰረተ ልማቶችን ለመስራት የሚያስፈልግ ሀብት ሲገኝ ክልሎች ደግሞ ቦታ ሊያዘጋጁ እንደሚገባ ገልጸዋል።
ለማህበረሰቡ የሚጠቅሙ የልማት ስራዎችን ለመስራት ሀብት ሲገኝ የሚጠየቀው ካሳ ከልማት ስራው በላይ እንደሆነ አንስተዋል።
የካሳ ጉዳይ በአንዳንድ አካባቢዎች የልማት ስራዎች እንዳይከናወኑ ማድረጉን ጠቅሰው፤ ከዚህም አልፎ የመዝርፊያ ስልት እየሆነ ምምጣቱን ጠቁመዋል።
በዚህም ልማት ለማምጣት አለመቻሉን እና ልማት ከተጀመረ በኋላ በካሳ ምክንያት የልማት ስራዎች እንደሚቋረጡ ገልጸው፤ ይህንንም ለመከላከል ሕግ ማውጣት ማስፈለጉን ተናግረዋል።
በመሆኑም ለማሕበረሰቡ በሚሰራ ፕሮጀክቶች ሁሉም አካል ትብብር ሊያደርግ ይገባል ብለዋል።
በዮናስ ጌትነት
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!