አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የአፈር ለምነትን ለመጠበቅና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ያስችላል አለ የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት፡፡
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ንጉሴ ደቻሳ (ፕ/ር) እንዳሉት÷ በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ለምግብነት የሚውሉ ችግኞችን በመትከል የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በትኩረት መስራት ይገባል፡፡
መርሐ ግብሩ የካርቦን ልቀትን ለመቀነስና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚያግዝ መሆኑን ጠቅሰው÷ የአፈር ለምነትን ለመጠበቅ አስተዋጽኦ እንዳለውም አንስተዋል።
ኢንስቲትዩቱ በዛሬው ዕለት በቢሾፍቱ ግብርና ምርምር ማዕከል የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብርን ማስጀመሩን የተናገሩት ዋና ዳይሬክተሩ ÷በሀገሪቱ ባሉት 23ቱም ማዕከላት መርሐ ግብሩ እንደሚከናወን ጠቁመዋል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ የደን ሽፋን ለመጨመር የአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም ወሳኝ እንደሆነ መጠቀሱን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ንጉሴ ደቻሳ (ፕ/ር) ሁሉም ሕብረተሰብ በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በመሳተፍ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡