ቢዝነስ

ከሕዳሴ ግድብ 5 ሺህ 895 ቶን የዓሣ ምርት ተገኘ

By Melaku Gedif

July 05, 2025

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚገኘውን የዓሣ ምርት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው አለ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ።

በቢሮው የእንስሳትና ዓሣ ሃብት ልማት ዳይሬክተር አቶ ሃይሉ ይርጋ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት፥ የሌማት ትሩፋት በክልሉ የዓሣ ሃብት ልማትን ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል፡፡

የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ በዓመት 15 ሺህ ቶን ዓሳ ማምረት የሚያስችል አቅም በክልሉ እንዳለ በጥናት መለየቱን አመልክተዋል፡፡

የፊታችን መስከረም ወር ላይ የሚመረቀው የሕዳሴ ግድብ ለዓሣ ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡

በግድቡ ሰው ሠራሽ ሐይቅ ለሚከናወነው የዓሣ ልማት ሥራ አስፈላጊው ድጋፍ እና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡

በበጀት ዓመቱ በአጠቃላይ 849 ወጣቶች በ35 የዓሣ መንደሮች መደራጀታቸውን ጠቅሰው÷ ከእነዚህ መካከልም 547ቱ ወደ ሥራ ገብተው ተጠቃሚ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡

ለማህበራቱ በዓሣ ማስገሪያ መረብና በዓሣ ምግብ አሰራር እንዲሁም ዓሣ የማስገር ክህሎት እንዲያዳብሩ የሚያስችል ስልጠና መሰጠቱን ጠቁመዋል።

ከተለያዩ አካላት በተገኘ ድጋፍም ለዓሣ ማስገሪያ የሚውሉ 54 ጀልባዎችና 1 ሺህ 600 መረቦችን ማቅረብ መቻሉን አብራርተዋል፡፡

በ2017 በጀት ዓመትም ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሰው ሰራሽ ሐይቅና ሌሎች 5 ሺህ 895 በላይ ቶን በላይ የዓሣ ምርት መመረቱን ጠቅሰዋል፡፡

በመላኩ ገድፍ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!