የሀገር ውስጥ ዜና

ለዓመቱ የተያዘው 5 ቢሊየን ችግኝ የመትከል እቅድ መሳካቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ገለፁ

By Tibebu Kebede

August 12, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 6፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በባህርዳር ከተማ በተካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ተሳትፈዋል።

በዚህ ወቅት ባደረጉት ንግግር ለዓመቱ የክረምት ወቅት የተያዘው 5 ቢሊየን ችግኝ የመትከል መርሃ ግብር በውቢቷ ሀዋሳ ከተማ ተጀምሮ በውቢቷ ባህርዳር ከተማ ተሳክቷል ብለዋል።