የሀገር ውስጥ ዜና

በአማራ ክልል የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጀመረ

By Hailemaryam Tegegn

July 08, 2025

በዚህም 13 ነጥብ 8 ሚሊየን የህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ እንደሚሆን ገልጸው፥ የበጎ ፈቃድ አገልገሎቱ የክልሉ መንግስት ሊያወጣው የሚችለውን ከ7 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በላይ እንደሚያድን አስረድተዋል፡፡

በአገልገሎቱ ትግበራ ሂደት በክልሉ ትኩረት የሚሹና የርብርብ ማዕከል ሊሆኑ ይገባል የተባሉ 14 የበጎ ፈቃድ ስራዎች መለየታቸውንና ሌሎች ተጨማሪ ሦስት የስምሪት መስኮች መለየታቸውንም ጠቁመዋል፡፡

የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር፣ የቤት ግንባታ እና ጥገና አገልገሎቶች፣ የደም ልገሳ፣ የማዕድ ማጋራት፣ የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርቶችና ነፃ የህክምና አገልግሎት ትኩረት የተሰጣቸው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዘርፎች መሆናቸውን ነው ነው ኃላፊው የገለጹት፡፡

የኮደርስ ስልጠና፣ የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማት እንዲሁም የትውልድ ግንባታ ሌሎች ትኩረት የተሰጣቸው ጉዳዮች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

በክልሉ ከ65 በመቶ በላይ የሚሆነው የህብረተሰብ ከፍል ወጣት መሆኑን የጠቁሙት ሃላፊው÷ እነዚህ ወጣቶች በበጎ ፈቃድ አግልገሎቱ እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በሚኪያስ አየለ