የሀገር ውስጥ ዜና

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በናይጄሪያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ሙሃማዱ ቡሃሪ ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ

By Yonas Getnet

July 13, 2025

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 6 ፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በናይጄሪያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ሙሃማዱ ቡሃሪ ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላፉት የሃዘን መግለጫ ፥በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ ስም ለሙሃማዱ ቡሃሪ ቤተሰብ፣ ለናይጄሪያ ሕዝብ እና መንግስት መጽናናትን ተመኝተዋል።