ቢዝነስ

ድርጅቱ በበጀት ዓመቱ 25 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ገቢ አገኘ

By Tibebu Kebede

August 12, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 6፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎትድርጅት በ2012 በጀት ዓመት 25 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ።

የ2012 በጀት ዓመት በተለይ የአፈር ማዳበሪያና ስንዴን የማጓጓዝ ስራ በመሰራቱ ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበበትና ስኬታማ የሆነበት ዓመት መሆኑን የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሮባ መገርሳ ተናግረዋል።