BERLIN, GERMANY - SEPTEMBER 24: Tigist Assefa from Ethiopia celebrating after crossing the finish line and set a new world record of 2:11:53h during the 2023 BMW Berlin-Marathon on September 24, 2023 in Berlin, Germany. (Photo by Luciano Lima/Getty Images)

ስፓርት

አትሌት ትዕግስት አሰፋ በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያን ትወክላለች

By Hailemaryam Tegegn

July 22, 2025

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አትሌት ትዕግስት አሰፋ በጃፓን ቶኪዮ በሚካሄደው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያን በመወከል ትወዳደራለች።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከአሠልጣኟ ጋር ባደረገው ውይይት አትሌት ትዕግስት በዓለም ሻምፒዮና ላይ ሀገሯን በመወከል እንድትሳተፍ ከስምምነት ላይ መደረሱን ገልጿል።

በአሁኑ ስዓት አትሌቷ በጥሩ አቋም ላይ በመሆኗ ክብረወሰን በማሻሻል የኢትዮጵያ ስም ከፍ ለማድረግ በማሰብ ጥሪውን መቀበሏን አሠልጣኟ ገመዶ ደደፎ ተናግረዋል፡፡

የፓሪስ ኦሎምፒክ የብር ሜዳልያ የለንደን ማራቶን አሸናፊዋ ትዕግስት አሰፋ በሻምፒዮናው ላይ እንድትሳተፍ ለቀረበላት ጥያቄ ለሰጠችው በጎ ምላሽ ፌዴሬሽኑ ምስጋና አቅርቧል።