አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 7፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኬንያ እየጨመረ የመጣውን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ተከትሎ አንድ ከፍተኛ የጤና ባለሥልጣን በኮቪድ 19 ህይወታቸው አልፏል ።
ካማኡ ሙጌንዳ የተባሉት እኝህ ባለስልጣን÷ በኬንያ የህክምና ምርምር ኢንስቲትዩት ምክትል ሃላፊ ከመሆናቸውም ባለፈ የሀገሪቱን የኮቪድ -19 ወረርሽኝ የምርመራ እና የክትባት ሙከራ መርሃ-ግብር በበላይነት ይመሩ ነበርም ተብሏል።