የሀገር ውስጥ ዜና

በሀዋሳ የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በተቋቋመ ጊዜያዊ ችሎት አንድ ግለሰብ በ3 ዓመት እስራት ተቀጣ

By Adimasu Aragawu

July 26, 2025

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 19፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በሀዋሳ ከተማ አየተከበረ ባለው ዓመታዊ የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል በተቋቋመ ጊዜያዊ ችሎት አንድ ግለሰብ በሦስት ዓመት እስራት ተቀጣ።

ግለሰቡ ዛሬ ማለዳ ስልክ ነጥቆ ሊያመልጥ ሲል በቁጥጥር ስር መዋሉን የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የወንጀልና ትራፊክ አደጋ ኃላፊ ኢንስፔክተር ሽመልስ ብሩ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል።

ከንግስ በዓል ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጸጥታና ህገ ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከልና ህግን ለማስከበር ከትላንት ከሰዓት ጀምሮ ጊዜያዊ የምድብ ችሎት ተቋቁሞ እየሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በዚህም የተቋቋመው ጊዜያዊ ችሎት ግለሰቡ የፈጸመውን ወንጀል አጣርቶ የሦስት ዓመት እስራት እንደተፈረደበት ማወቅ ተችሏል።

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ ፌደራል ፖሊስ እና የክልል ፖሊስ በጋራ በመሆን ከአንድ ማዕከል በተሰጠ አቅጣጫ የፀጥታ ማስከበር ስራውን እየሰሩ መሆናቸውን ኢንስፔክተር ሽመልስ አስረድተዋል።

ጊዜያዊ ችሎቱም ከሌሎች አካባቢዎች የመጡ እንግዶችን ታሳቢ አድርጎ ፍትህን ለማፋጠን የተቋቋመ ስለመሆኑም ተገልጿል።

በመቅደስ አስፋው

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!