የሀገር ውስጥ ዜና

የአፋር ክልል ምክር ቤት 7 ቢሊየን ብር በላይ ሆኖ የቀረበለትን የ2013 በጀት አጸደቀ

By Meseret Demissu

August 13, 2020

አዲስ አበባ ፣ነሀሴ 7 ፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት የስራ ዘመን አስረኛ መደበኛ ጉባኤ ለ2013 ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ሆኖ የቀረበለትን የ2013 በጀትና የተለያዩ ሹመቶችን አጸደቀ።

የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ መሐመድ ሃሰን÷ የክልሉን የ2012 ዓ.ም የስራ አፈጻጸምና ተያያዥ ወቅታዊ ሀገራዊና ክልላዊ ሁኔታዎችን ታሳቢ በማድረግ በጀቱ መዘጋጀቱን ተናግረዋል ።