የሀገር ውስጥ ዜና

የመዲናዋ የኮሪደር ልማት የፈጠራ እና የፍጥነት ውጤት ማሣያ ነው – አቶ ሙስጠፋ መሐመድ

By Abiy Getahun

August 03, 2025

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት የከተማዋን ገጽታ የቀየረ የፈጠራ እና የፍጥነት ውጤት ማሣያ ነው አሉ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፋ መሐመድ፡፡

የብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት አባላት ከእንጦጦ እስከ 4 ኪሎ ፕላዛ፣ የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቪሽንና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ጎብኝተዋል፡፡

አቶ ሙስጠፋ መሐመድ በጉብኝቱ ወቅት እንዳሉት፤ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት የከተማዋን ገጽታ የቀየረ ነው፡፡

የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽን የኢትዮጵያን መጻኢ ተስፋ የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመው፤ ኢትዮጵያ ወደ ዘላቂ ልማት ለምታደርገው የለውጥ ጉዞ ታላቅ ምዕራፍ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

የተመለከቷቸው የልማት ፕሮጀክቶች የፍጥነትና የፈጠራ ውጤቶች መሆናቸውን ጠቁመው፤ ከሥራ ፈጠራ እና ከሌሎችም አኳያ የህዝቡን ኑሮ የቀየሩ ናቸው ብለዋል።

በሀገር ደረጃ ተግባራዊ የተደረጉ ሁሉም ኢኒሼቲቮች በሶማሌ ክልል መጀመራቸውን ገልጸው፤ የጅግጅጋ ከተማ የኮሪደር ልማት ስራዎች በቅርቡ እንደሚመረቁ መግለጻቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።

የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በክልሉ የማደራጀት ስራዎች መጀመራቸውን ጠቁመው፤ የገጠር ኮሪደር፣ የሌማት ትሩፋት እንዲሁም በአረንጓዴ ዐሻራ ውጤታማ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!