የሀገር ውስጥ ዜና

በክልሉ ከ2 ሺህ 600 በላይ የትምህርት ቤት አመራሮችና መምህራን የአቅም ግንባታ ስልጠና እየወሰዱ ነው

By Adimasu Aragawu

August 06, 2025

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 254 የትምህርት ቤት አመራሮችና 2 ሺህ 359 መምህራን የክረምት ልዩ አቅም ግንባታ ስልጠና እየወሰዱ ነው።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ልማት ዳይሬክተር አቶ ባህሩ ዓለሙ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ መምህራንና አመራሮቹ በአምስት ዩኒቨርሲቲዎች ስልጠናውን እየተከታተሉ ይገኛሉ።

ስልጠናው መምህራን በሚያስተምሯቸው የትምህርት ዓይነቶች የሚሰጥ መሆኑን አንስተው÷ ከመምህራን ማስተማር ጋር ቀጥታ የተገናኘ በማስተማር ስነ ዘዴ ላይ ያተኮረ ነው ብለዋል።

በተጨማሪም ቴክኖሎጂን ለመማር ማስተማር ስራ እንዲጠቀሙ የሚያስችል ስልጠና እንደሚሰጥ ጠቅሰው÷ መምህራን ብቁ ሆነው ዕውቀታቸውን ለተማሪዎቻቸው ማስተላለፍ የሚችሉበትን ዕድል ይፈጥራል ነው ያሉት።

በዩኒቨርሲቲና ኮሌጆች የተዘጋጀ ሞጁሎችን በመጠቀም የትምህርት አመራሮች በመማር ማስተማር ስራ ላይ ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ የሚያስችል ስልጠናው እንደሚሰጣቸውም አመልክተዋል።

ስልጠናው የትምህርት ጥራት ችግርን ለመፍታት በቀጥታ ከተማሪዎች ጋር የሚገናኙ መምህራን እና አመራሮች ከሚያስተምሩት የትምህርት ይዘት ጋር በተናበበ መልኩ የሚሰጥ በመሆኑ ከፍተኛ አስተዋጽዖ አለው ብለዋል።

በአድማሱ አራጋው

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!