ስፓርት

ቲሞቲ ዊሃ ማርሴን ተቀላቀለ

By Abiy Getahun

August 07, 2025

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የቀድሞ እግር ኳስ ኮከቡ ጆርጅ ዊሃ ልጅ ቲሞቲ ዊሃ የፈረንሳዩን ክለብ ኦሎምፒክ ደ ማርሴን በይፋ ተቀላቅሏል፡፡

የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን የፊት መስመር ተጫዋች ቲሞቲ ዊሃ ከጣሊያኑ ክለብ ጁቬንቱስ ወደ ኦሎምፒክ ደ ማርሴ አምርቷል፡፡

የ25 ዓመቱ ተጫዋች በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ለጁቬንቱስ ባደረጋቸው 30 የጣሊያን ሴሪ አ ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሮ ሁለት ለግብ የሚሆን ኳስ አመቻችቶ አቀብሏል፡፡

ቲሞቲ ዊሃ በ2023/24 የውድድር ዓመት ከፈረንሳዩ ክለብ ሊል ጁቬቱስን መቀላቀቀሉ ይታወሳል፡፡

ከእግር ኳስ ህይወቱ በኋላ ወደ ፖለቲካው ዓለም በመግባት ሀገሩን ላይቤሪያ በፕሬዚዳንትነት ያገለገለገው አባቱ ጆርጅ ዊሃ የባሎንዶር ሽልማትን ያሸነፈ ብቸኛ አፍሪካዊ ተጫዋች መሆኑ ይታወቃል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!