የሀገር ውስጥ ዜና

ጉዳት የደረሰበትን የጊደብ ወንዝ ድልድይ በፍጥነት ወደ አገልግሎት ለመመለስ እየተሰራ ነው

By Yonas Getnet

August 10, 2025

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ጉዳት የደረሰበትን የጊደብ ወንዝ ድልድይ በፍጥነት ወደ አገልግሎት ለመመለስ እየተሰራ ነው አለ።

ከደብረማርቆስ ወደ ባሕር ዳር በሚወስደው መንገድ ላይ የሚገኘው የጊደብ ወንዝ ድልድይ ትናንት ሌሊት በጣለው ከባድ ዝናብ ባጋጠመው ጎርፍ ጉዳት ደርሶበታል።

በመንገዶች አስተዳደር የደብረማርቆስ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ምህንድስና ኦፕሬሽን ቡድን መሪ መንግስቱ አስረስ በጎርፍ አደጋ የደረሰው ጉዳት ከደብረማርቆስ ወደ ባሕር ዳር የሚወስደውን መንገድ የትራንስፖርት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ እንዲስተጓጎል ማድረጉን ተናግረዋል።

ዲስትሪክቱ ተገጣጣሚ ድልድይ በፍጥነት በመገንባት የትራንስፖርት አገልግሎት ወደ ነበረበት ለመመለስ ጥረት እያደረገ መሆኑን ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን አስረድተዋል።

በበላይነህ ዘለዓለም

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!