አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት ለብርሃን አይነ ሥውራን አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የብሬል ፕሪንተር፣ ዲጂታል ሪከርድስ እና ሌሎች ቁሶችን ድጋፍ አድርጓል፡፡
የቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት ትምህርት ትውልድን ለማነጽና ለነገ ሀገር ተረካቢ የሆነ የተማረ ዜጋን ለማፍራት ወሳኝ ተግባር በመሆኑን አመልክቷል፡፡
ለዚህም ጽ/ቤቱ በትምህርት ዘረፍ ላይ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ላለፉት 5 ዓመታት 35 ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶችን በመላ ሀገሪቱ ገንብቶ በርካታ ተማሪዎች የትምህርት አገልግሎት እንዲያገኙ አድርጓል፡፡
የጥራት ደረጃቸውን ጠብቆ ከገነባቸው እጅግ ዘመናዊ ት/ቤቶች ውስጥ አንዱ አዲስ አበባ ከተማ የሚገኘው ብርሃን የአይነ ሥውራን አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ነው፡፡
ትምህርት ቤቱ ከ400 በላይ የሆኑ ተማሪዎችን ከተለያዩ አካባቢዎች ተቀብሎ በማስተማር ላይ ይገኛል፡፡
የቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት የት/ቤቱን የመማር ማስተማር ሒደት፣ የት/ቤቱን እና የተማሪዎቹን ፍላጎት በቅርብ ክትትል በማድረግ በርካታ ተጨማሪ ድጋፎችን እያደረገ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡
በዛሬው ዕለትም የመማር ማስተማር ሒደቱን ሊያቀላጥፉ የሚችሉ የብሬል ፕሪንተር (ኢምቦሰር) እና ዲጂታል ሪከርድስ ድጋፍ አድርጓል፡፡
በተጨማሪም በት/ቤቱ ውስጥ ለተማሪዎች አገልግሎት በመስጠት ላይ ለሚገኘው ክሊኒክ የተለያዩ የሕክምና መሳሪያዎች እና መመርመሪያ ሪኤጀንቶችን አበርከቷል፡፡
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!