የሀገር ውስጥ ዜና

በኦሮሚያ ክልል የ32 ሚሊየን መማሪያ መጻሕፍት ሕትመት ሥራ…

By Melaku Gedif

August 14, 2025

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኦሮሚያ ክልል ለ2018 ትምህርት ዘመን ከ32 ሚሊየን በላይ የመማሪያ መጻሕፍትን ለማሳተም ታቅዶ ሥራ ተጀምሯል አለ የክልሉ ትምህርት ቢሮ፡፡

የቢሮው ም/ኃላፊ ቡልቶሳ ኢርኮ (ዶ/ር) ለፋና ዲጂታል እንዳሉት ÷ በቀጣዩ ዓመት የመማር ማስተማር ሒደቱን ለማሳለጥ አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡

በዓመቱ ለቅደመ መደበኛ፣1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት የመማሪያ መጻሕፍትን አቅርቦት ለማሟላት በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

በዚህ መሰረትም ከ32 ሚሊየን በላይ መጻሕፍትን ለማሳተም ታቅዶ ከአሳትሚ ድርጅቶች ጋር ውል ተይዞ የሕትመት ሥራ መጀመሩን ነው ያስረዱት፡፡

በሌላ በኩል የመማሪያ ክፍሎችን ለትምህርት ዝግጁ የማድረግና ሌሎች ተያያዥ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡

በክልሉ የተጀመረውን የተማሪዎች ምገባ አገልግሎት አጠናክሮ ለማስቀጠል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡

በትምህርት ዘመኑ የግብዓት እጥረት እንዳይከሰትና ሁሉም ተማሪዎች በትምህርት ገበታቸው እንዲገኙ አስፈላጊው ክትትል እንደሚደረግም አመልክተዋል፡፡

በመላኩ ገድፍ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!