የሀገር ውስጥ ዜና

ሉሲ በቼክ ሪፐብሊክ ፕራግ ሙዚዬም ለዕይታ ልትቀርብ ነው

By Melaku Gedif

August 15, 2025

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ)የኢትዮጵያ ምድረ ቀደምት ማሳያ የሆኑት ሉሲ እና ሰላም በቼክ ሪፐብሊክ በሚገኘው ፕራግ ሙዚዬም ለዕይታ ሊቀርቡ ነው።

የኢትዮጵያን ምድረ ቀደምትነት የሚያስተዋውቅ ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽን በፈረንጆቹ የፊታችን ነሐሴ 25 ጀምሮ በመካከለኛው አውሮፓ ይካሄዳል።

በዚህም የኢትዮጵያ ምድረ ቀደምት ማሳያ የሆኑት ሉሲና ሰላም በቼክ ሪፐብሊክ በሚገኘው ፕራግ ሙዚዬም ለዕይታ ይቀርባሉ።

በተጨማሪም የኢትዮጵያን ሃብቶች የሚያስተዋውቁ የቢዝነስ ፎረሞች፣ የጥበብ ሥራዎች ኤግዚቢሽንና ሌሎች መድረኮች ይካሄዳሉ።

የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ በሉሲና ሰላም ቅሪተ አካላት ሽኝት መርሐ ግብር ላይ እንዳሉት ፥ ኤግዚቢሽኑ አዲሲቷን ኢትዮጵያ የምንገልጽበት ነው ።

የፕራግ ሙዚዬም ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚካኤል ሉቸክ በበኩላቸው ፥ መርሐ ግብሩ የዓለም የሰው ዘር መገኛ የሆነችው የኢትዮጵያን ምድረ ቀደምትነት የምናሳይበት በመሆኑ ታሪካዊ ሁነት ነው ብለዋል።

በቅድስት አባተ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!