የሀገር ውስጥ ዜና

ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ለመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

By Hailemaryam Tegegn

September 04, 2025

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።

ፕሬዚዳንት ታዬ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፥ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1 ሺህ 500ኛው የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ብለዋል።

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የትሩፋት እንዲሆን ከልብ እመኛለሁ ሲሉም መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።