የሀገር ውስጥ ዜና

ተወዳዳሪና ዘመኑን የዋጀ ትውልድ ለመቅረጽ እየተሰራ ነው – አቶ ደስታ ሌዳሞ

By Melaku Gedif

September 04, 2025

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ተወዳዳሪ እና ዘመኑን የዋጀ እውቀት ያለው ትውልድ ለመቅረጽ በትኩረት እየተሰራ ነው አሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፡፡

በክልሉ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ልዩ የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ማጠቃለያ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ተካሂዷል፡፡

አቶ ደስታ ሌዳሞ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ በ2018 የትምህርት ዘመን ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት ተደራሽ ለማድረግ አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ነው፡፡

በተለይም የመማሪያ መጽሐፍትን ጨምሮ ሌሎች የትምህርት ግብዓቶች በበቂ ሁኔታ እንዲሰራጩ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

ተማሪዎች የነገ ሀገር ተረካቢዎች መሆናቸውን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ ÷ ለዚህም ተወዳዳሪ፣ ብቁና ዘመኑን የዋጀ እውቀት እንዲሸምቱ በቅንጅት መስራት ይገባል ብለዋል፡፡

በክልሉ የተሰጠው ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት ሀገርን የሚገነቡ ተማሪዎችን ለመቅረጽ ከፍተኛ ሚና እንዳለው አስረድተዋል፡፡

ተማሪዎች በቀጣዩ ሀገር አቀፍ ፈተና የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ትምህርታቸውን በትኩረት እንዲከታተሉ ማሳሰባቸውንም የርዕሰ መስተዳድሩ ጽ/ቤት የዲጂታል ቴክኖሎጂና ሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ታደሰ ለፋና ዲጂታል ገልጸዋል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!