አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼህ መሃሙድ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕከት፥ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼህ መሃሙድን ዛሬ ጠዋት አግኝቼ የጋራ ፍላጎት ባለን ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተናል ብለዋል።
በውይይታቸው በቀጣናችን ፀጥታና መረጋጋት ብሎም ልማትን ለማረጋገጥ ያለንን ፅኑ አቋም በድጋሚ አረጋግጠናል ነው ያሉት፡፡