ስፓርት

20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ነገ በቶኪዮ ይጀመራል

By Melaku Gedif

September 12, 2025

አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በነገው ዕለት በጃፓን ቶኪዮ ከተማ በይፋ ይጀመራል፡

ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው ከ800 ሜትር ጀምሮ እስከ ማራቶን ባሉ ርቀቶች እንዲሁም በእርምጃ ውድድር በሁለቱም ጾታ ትሳተፋለች፡፡

በውድድሩ የሚሳተፉ ኢትዮጵያውያን አትሌቶችም በተለያየ ዙር ወደ ጃፓን ቶኪዮ ከተማ አቅንተዋል፡፡

ቀደም ሲል ቶኪዮ የገባው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ በትናንትናው ዕለት የመጀመሪያውን ልምምድ አድርጓል፡፡

ከመስከረም 3 እስከ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በቶኪዮ በሚካሄደው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከተለያዩ ሀገራት የተወጣጡ 2 ሺህ በላይ አትሌቶች ይሳተፋሉ፡፡

በሻምፒዮናው በ49 ዘርፎች ውድድር የሚካሄድ ሲሆን ÷147 ሜዳልያዎችም ለአሸናፊ አትሌቶች የሚበረከቱ ይሆናል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!