አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዘንድሮ ዓመት ሬሜዲያል (የአቅም ማሻሻያ) መርሐ ግብር ይኖራል አሉ የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)።
የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ውጤትን በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከባለፈው ዓመት መግቢያውን ከፍ በማድረግ ሬሜዲያል ፕሮግራም ይሰጣል ብለዋል።
ወደ ሬሜዲያል ፕሮግራም ምን ያህል ተማሪዎች እንደሚገቡ አለመወሰኑን ገልጸው÷ ዘንድሮ እድል ለሚሰጣቸው ተማሪዎች መግቢያው ካለፈው ዓመት ከፍ እንደሚደረግ ጠቁመዋል።
በመርሐ ግብሩ ተጠቃሚ የሚሆነው የተማሪ ቁጥር ላይ ቅናሽ እንደሚኖረውም አመልክተዋል።
በዮናስ ጌትነት
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!