የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በስፖርት ዘርፍ በትብብር ለመስራት ተስማሙ

By Abiy Getahun

September 15, 2025

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በስፖርት ዘርፍ በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል፡፡

የባህል እና ስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ ነፊሳ አልማህዲ ከሩሲያ ስፖርት ፌዴሬሽን ሚኒስትር ሚካኤል ዴግትያረቭ ጋር በትብብር ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተወያይተዋል፡፡

ሚኒስትር ዴዔታዋ በወቅቱ እንዳሉት፤ የረጅም ጊዜ ግንኙነት ያላቸው ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በተለያዩ ዘርፎች በትብብር እየሰሩ ነው።

ይህንን ትብብር በስፖርት ዘርፍም አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ በስፖርት ልማት ዘርፍ ስልጠናዎች፣ ስፖርት ሳይንስ፣ ስነ-ምግብና ስፖርት አካዳሚ አስተዳደር እንዲሁም በቴክኖሎጂ ሽግግር በትብብር ለመስራት ፍላጎት እንዳላት ገልፀዋል።

ሚካኤል ዴግትያረቭ በበኩላቸው ግንኙነታችንን በማጠናከር በስፖርት ዘርፍ በጋራ እንሰራለን ብለዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!