አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የዶዶላ ኢፈ ቦሩ ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪ የሆነው ካሊድ በሽር በ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና 591 በማምጣት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል፡፡
እንደ ኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ መረጃ ተማሪ ካሊድ በሽር እንግሊዘኛ 96፣ ሒሳብ 100፣ ፊዚክስ 100 ኬሚስትሪ 98፣ ባዮሎጂ 99፣ አፕቲትዩድ 98 አምጥቷል፡፡
የዶዶላ ኢፈ ቦሩ ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ርዕሰ መምህር ደቱ ዲቦ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት ÷ ተማሪ ካሊድ በሽር በትምህርቱ በጣም ጎበዝ፣ ጥሩ ሥነ ምግባር ያለው እና አርአያ የሆነ ተማሪ ነው፡፡
በ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት በማምጣቱ መደሰታቸውንም ገልጸዋል፡፡
በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ፈተናን ከወሰዱ ተማሪዎች ውስጥ 8 ነጥብ 4 በመቶ ተማሪዎች ብቻ ናቸው ከ50 በመቶ በላይ ውጤት በማምጣት ያለፉት፡፡
50 ት/ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ያሳለፉ ሲሆን ÷1 ሺህ 249 ት/ቤቶች ደግሞ ምንም ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም፡፡
በመላኩ ገድፍ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!