የሀገር ውስጥ ዜና

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራሮች ጋር ተወያዩ

By Adimasu Aragawu

September 15, 2025

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አዲስ ከተመረጠው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ ሀገር አቀፍ የመጅሊስ ምርጫው በተሳካ መልኩ እንዲካሄድ በማድረጋቸው ለሕዝበ ሙስሊሙና ለምክር ቤቱ አመራሮች አድናቆቴን ለመግለጽ እወዳለሁ ብለዋል።

የመጅሊስ ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ፣ አካታችና አሳታፊ በሆነ መልኩ መከናወኑ ትምህርት የሚሰጥ መሆኑንም አመልክተዋል።

መንግሥት ከጠቅላይ ምክር ቤቱ አመራሮች ጋር በጋራ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ይበልጥ ተቀራርቦ የሚሠራ ሲሆን÷ በሚያስፈልገው ሁሉ የሚጠበቅበትን ድጋፍ ያደርጋል ሲሉም ጠቁመዋል።

ለምክር ቤቱ አመራሮች መልካም የአገልግሎት ዘመን እንዲሆንላቸው ምኞታቸውን ገልጸዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!