የሀገር ውስጥ ዜና

አለም ዓቀፉ የህፃናት አድን ድርጀት ለባህርዳር ከተማ የ42 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ

By Tibebu Kebede

August 16, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 10፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አለም ዓቀፍ የህፃናት አድን ድርጅት ለባህርዳር ከተማ የኮሮና ቫይረስ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚውል 42 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ።

በተደረገው ድጋፍ ዙሪያ የክልሉ የኮሮና ቫይረስ መከላከል እና መቆጣጠር ግብረ ሀይል አስተባባሪ ዶክተር ሙሉነሽ አበበ፣ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ እና የባህርዳር ከተማ ክፍለ ከተሞች ኃላፊዎች በተገኙበት ወይይት ተደርጓል።