አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 10፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አለም ዓቀፍ የህፃናት አድን ድርጅት ለባህርዳር ከተማ የኮሮና ቫይረስ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚውል 42 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ።
በተደረገው ድጋፍ ዙሪያ የክልሉ የኮሮና ቫይረስ መከላከል እና መቆጣጠር ግብረ ሀይል አስተባባሪ ዶክተር ሙሉነሽ አበበ፣ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ እና የባህርዳር ከተማ ክፍለ ከተሞች ኃላፊዎች በተገኙበት ወይይት ተደርጓል።