ስፓርት

በመርሲሳይድ ደርቢ ሊቨርፑል ኤቨርተንን 2 ለ 1 አሸነፈ

By Mikias Ayele

September 20, 2025

አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ5ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ ሊቨርፑል ኤቨርተንን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡

በአንፊልድ በተደረገው ጨዋታ ሪያን ግራቨንበርች እና ሁጉ ኢኪቲኬ የሊቨርፑልን ጎሎች ሲያስቆጥሩ የኤቨርተንን ብቸኛ ጎል ኤዲሪሳ ጉየ አስቆጥሯል፡፡

ውጤቱን ተከትሎም ሊቨርፑል ነጥቡን ወደ 15 ከፍ በማድረግ መሪነቱን አጠናክሯል፡፡