አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የማሽቃሮን ዕሴት በማዳበር ለልማትና ለሕብረ ብሔራዊ አንድነት ግንባታ ማዋል ይገባል አሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)።
የካፈቾ ብሔር የዘመን መለወጫ “ማሽቃሮ” በዓል ከፍተኛ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች በተገኙት የነገስታት መናገሻ በሆነው “ቦንጌ ሻምበቶ” ተከብሯል።
ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በበዓሉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት÷ የማሽቃሮ ዕሴት የሆኑ አብሮነትና አንድነትን በማጠናከር ለልማትና ለሕብረ ብሄራዊ አንድነት ግንባታ ማዋል ይገባል ብለዋል።
የካፈቾ ብሔር ድንቅ የተፈጥሮ ጥበቃ ባህል ባለቤት መሆኑን አንስተው÷ የብሔረሰቡ ድልብ የእውቀትና ጥበብ መገለጫ የሆነውን ማሽቃሮ በመጠበቅ እና በማልማት ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተዋል።
የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በበኩላቸው÷ ማሽቃሮ የአብሮነት፣ አንድነት እና እርቅ መገለጫ መሆኑን አንስተው÷ በዓሉ በዩኔስኮ እንድሚዘገበ እንቅስቃሴ መጀመሩን ተናግረዋል።
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!