ጤና

የጤና ባለሙያዎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አገልጋይና ተገልጋይን ያማከለ አገልግሎት…

By Adimasu Aragawu

September 30, 2025

አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን የበለጠ ከማስፋት በተጓዳኝ የጤና ባለሙያዎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አገልጋይና ተገልጋይን ያማከለ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ትኩረት ተደርጓል አሉ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ።

ሚኒስትሯ ይህን ያሉት ለቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ህክምና ኮሌጅ የህክምና ባለሙያዎች ሁለት ባለ 16 እና አንድ ባለ 12 ወለል የመኖሪያ ህንጻዎች ግንባታን ባስጀመሩበት ወቅት ነው።

የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታልና ኮሌጁ በአገልግሎት አሰጣጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚያደርጋቸውን የተለያዩ የሪፎርም ስራዎችን እየተገበሩ ነው ብለዋል።

በሆስፒታሉም ሆነ በኮሌጁ በኩል የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀልጣፋና እርካታ የሚሰጡ መሆን እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።

ጤና ባለሙያዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው÷ ለዚህም መንግሥት አገልጋይና ተገልጋይን ያማከለ የአገልግሎት አሰጣጥ ስትራቴጂን በመተግበር ጥያቄያቸውን ደረጃ በደረጃ ለመፍታት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የጤና ባለሙያዎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመነጋገር መፍትሔ ለመስጠት በቁርጠኝነት እየሰራን ነው ማለታቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!