ቢዝነስ

ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅቷን አጠናቀቀች

By Adimasu Aragawu

October 07, 2025

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅቷን አጠናቅቃለች አለ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር።

የዝግጅቱ መጠናቀቅና የግብይት ማስጀመሪያ መርሐ ግብርን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴዔታ ያስሚን ወሃብረቢ የስምምነቱ ትግበራ ለኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል፡፡

የግብይት ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ መስከረም 29 ቀን 2018 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑንም ጠቁመዋል።

በዚህም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎ ሥጋ፣ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም በየብስ ትራንፖርት ቡና፣ የጥራጥሬ ምርቶችና የቅባት እህሎች ወደ ኬንያ፣ ሶማሊያ እና ደቡብ አፍሪካ እንደሚላክ አብራርተዋል፡፡

አኅጉራዊ ነፃ የንግድ ስምምነት ትግበራ ለኢትዮጵያ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎች እንደሚኖሩት ጠቁመው÷ ለሀገር ውስጥ ንግድ ተወዳዳሪነትና ኢንቨስትመንት መነቃቃት፣ ለሸማቹ የተሻለ አማራጭና ሰፊ የምርት አቅርቦት እንዲሁም በአፍሪካ ሀገራት መካከል የገበያ ትስስርን ለማስፋት እንደሚያስችል ጠቅሰዋል፡፡

በቤተልሔም መኳንንት

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!