አዲስ አበባ፣ መስከረም 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2026 የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ 9ኛ ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጊኒ ቢሳውን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ራምኬል ጀምስ በመጀመሪያው አጋማሽ አስቆጥሯል፡፡
ዋልያዎቹ በማጣሪያው ካደረጓቸው 9 ጨዋታዎች ሁለቱን ሲያሸንፉ፤ በሶስቱ አቻ እንዲሁም በአራቱ ደግሞ ተሸንፈዋል፡፡
ከ2026ቱ ዓለም ዋንጫ ውድድር ውጪ መሆኑን አስቀድሞ ያረጋገጠው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በምድቡ 9 ነጥብ በመያዝ 5ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!