ስፓርት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጊኒ ቢሳውን አሸነፈ

By Abiy Getahun

October 08, 2025

አዲስ አበባ፣ መስከረም 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2026 የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ 9ኛ ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጊኒ ቢሳውን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ራምኬል ጀምስ በመጀመሪያው አጋማሽ አስቆጥሯል፡፡

ዋልያዎቹ በማጣሪያው ካደረጓቸው 9 ጨዋታዎች ሁለቱን ሲያሸንፉ፤ በሶስቱ አቻ እንዲሁም በአራቱ ደግሞ ተሸንፈዋል፡፡

ከ2026ቱ ዓለም ዋንጫ ውድድር ውጪ መሆኑን አስቀድሞ ያረጋገጠው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በምድቡ 9 ነጥብ በመያዝ 5ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!