አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ያካሄደው የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ውጤት ይፋ ሆኗል።
በጨረታ ሒደቱ 31 ባንኮች የተሳተፉ ሲሆን÷ በዚህም የምንዛሪ ጨረታ አንድ የአሜሪካን ዶላር ዋጋ በአማካኝ 148 ነጥብ 1007 ብር ሆኖ መመዝገቡ ተገልጿል፡፡
ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ ገበያን በመገምገም በቀጣይም ተመሳሳይ የውጭ ምንዛሪ ጨረታውን እንደሚቀጥል አመላክቷል፡፡
ከውጭ ምንዛሪ ገቢ ከፊሉን ለባንኮች በጨረታ ማቅረቡ በባንኮች ዘንድ የሚኖረውን የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት በመደገፍ የዋጋ እና የውጭ ምንዛሪ መረጋጋት እንዲፈጠር ማስቻሉን ባንኩ ጨረታውን አስመልክቶ ባወጣው መረጃ ገልጿል።
ብሔራዊ ባንክ በትናንትናው ዕለት 150 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ለውጭ ምንዛሪ ጨረታ ማዘጋጀቱን መግለጹ ይታወሳል።
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!