የሀገር ውስጥ ዜና

አምባሳደር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ፊት ቀርበው ቃለ መኃላ ፈጸሙ

By Adimasu Aragawu

October 14, 2025

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በጂቡቲ ሪፐብሊክ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሆነው የተሾሙት አምባሳደር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) የሹመት ደብዳቤያቸውን በመቀበል ቃለ መኃላ ፈጽመዋል።

አምባሳደሩ ከፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የሹመት ደብዳቤያቸውን በመቀበል የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ፊት ቀርበው ነው ቃለ መኃላ የፈጸሙት።

ፕሬዚዳንት ታዬ ለተሿሚ አምባሳደሩ የኢትዮጵያ እና ጂቡቲን ሁለንተናዊ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር የሚያስችሉ የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።

በሥነ ሥርዓቱ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ መታደማቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!