የሀገር ውስጥ ዜና

አየር ኃይል የትኛውንም ግዳጅ ለመፈፀም በላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል – ሌ/ጄ ይልማ መርዳሳ

By Melaku Gedif

October 15, 2025

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አየር ኃይል የሚሰጠውን ማንኛውንም ግዳጅ ለመፈፀም በላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል አሉ የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌ/ጄ ይልማ መርዳሳ፡፡

የአየር ኃይል ምክትል አዛዥ ለአየር ኦፕሬሽን በግዳጅ አፈጻጸም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ክፍሎች እውቅና ሰጥቷል፡፡

ሌ/ጄ ይልማ መርዳሳ በዚህ ወቅት÷ተቋሙ የሚሰጠውን ተልዕኮ እና ግዳጅ ለመፈፀም በከፍተኛ የዝግጁነት አቅም ላይ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል ።

አየር ኃይል በአጭር ጊዜ ባከናወናቸው የለውጥ ሥራዎች አስደናቂ ስኬቶችን አስመዝግቧል ያሉት ዋና አዛዡ ÷ ይህም የአመራሩና የአባላቱ የጋራ ሥራ ውጤት መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

አየር ኃይል ም/አዛዥ ለአየር ኦፕሬሽን ብ/ጄ ተስፋዬ ለገሰ በበኩላቸው÷ ክፍሉ የኢትዮጵያን የአየር ክልል በንቃት በመጠበቅ የተቋሙን የውጊያ ዝግጁነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ ግዳጃቸውን በብቃት ለተወጡ ክፍሎች የእውቅናና የምስጋና ሰርተፍኬት መሰጠቱንም የመከላከያ ሠራዊት ኦንላይን ሚዲያ ዋና አዘጋጅ ሌ/ኮ ውብሸት ቸኮል ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!