ቢዝነስ

የጋምቤላ ክልል ከ1 ሺህ 500 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ወደ ብሔራዊ ባንክ አስገባ ‎

By Abiy Getahun

October 16, 2025

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ‎የጋምቤላ ክልል ማዕድን ኤጀንሲ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ከ1 ሺህ 500 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ተደርጓል አለ፡፡ ‎ ‎የኤጀንሲው ምክትል ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ ገዳሙ እንዳሉት፤ በሩብ ዓመቱ 1 ሺህ 500 ኪሎ ግራም ወርቅ ገቢ ለማድረግ ታቅዶ ከዕቅድ በላይ ማሳካት ተችሏል።

በዚህም 1 ሺህ 588 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ተደርጓል ብለዋል። ‎ ‎ለብሔራዊ ባንክ ገቢ የተደረገው የወርቅ መጠን ከዓምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ682 ኪሎ ግራም ብልጫ ማሳየቱ ተመላክቷል፡፡ ‎ ‎በክልሉ በበጀት ዓመቱ 6 ሺህ ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ለማቅረብ እየተሰራ ስለመሆኑም አብራርተዋል፡፡ ‎ መንግሥት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረት ለብሔራዊ ባንክ የሚገባውን የወርቅ መጠንን ማሳደጉን ‎ገልጸው፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ሕገ ወጥ የወርቅ ግብይት እንዲቀንስ አድርጓል ነው ያሉት፡፡ ‎ ‎በክልሉ በዋናነት በአራት ወረዳዎች የወርቅ ማዕድን እንደሚመረትም ገልጸዋል። ‎ ‎በአብዱ ሙሃመድ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡- YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!