የሀገር ውስጥ ዜና

የኑሮ ውድነትን የማረጋጋትና ከተረጂነት የመላቀቅ ግቦችን ለማሳካት …

By Melaku Gedif

October 20, 2025

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኑሮ ውድነትን የማረጋጋትና ከተረጂነት የመላቀቅ ግቦችን ለማሳካት የባለድርሻ ተቋማት ቅንጅት ሊጠናከር ይገባል አሉ የብልጽግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ።

የብልጽግና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ግምገማ ዛሬም ቀጥሎ እየተካሄደ ነው፡፡

በመድረኩ በመንግሥት ሥራዎች አፈጻጸም ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን÷ የሥራ ዕድል ለመፍጠር፣ የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የተከናወኑ ሥራዎችና የተገኙ ውጤቶች እንዲሁም ከተረጂነት የመላቀቅ ግቦች በአጀንዳነት ቀርበዋል፡፡

አቶ አደም ፋራህ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ የኑሮ ውድነትን ማረጋጋትና ሥራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት የሚሹ አንገብጋቢ አጀንዳዎች ናቸው፡፡

ከተረጂነት መላቀቅ የተሟላ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መንገድ መሆኑን ገልጸው÷ በዚህ ላይ በተቀናጀ አግባብ መስራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

ሦስቱንም ሀገራዊ ግቦች በተሟላ መልኩ ለማሳካት የባለድርሻ ተቋማት ቅንጅት ሊጠናከር እንደሚገባ ነው የገለጹት፡፡

በአፈጻጸም ደረጃ እንደ ሀገር ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቁመው÷ያለውን የአፈጻጸም ልዩነት ለማጥበብ መስራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል፡፡

በዘርፉ ውጤታማነትን ለማሳደግ በጋራ ማቀድ እና አፈጻጸሞችን በጋራ በጥልቀት መገምገም ይገባል ማለታቸውንም ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!