የሀገር ውስጥ ዜና

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ

By Yonas Getnet

October 22, 2025

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ በዛሬው ዕለት መካሄድ ጀምሯል።

ጉባዔውን አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በፀሎት አስጀምረዋል።

በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት እንዳሉት፤ በተለያዩ መንገዶች እየተከናወኑ የሚገኙ ቤተክርስቲያንን የመዳፈር ተግባራት ለመፍታት በሕግ አግባብ መንቀሳቀስ ይገባል።

የነገ ትውልድ ልማታዊ ተስፋ እውን የሚሆነው ሰላምና አንድነት ሲኖር በመሆኑ ሁሉም ለሀገር ሰላምና አንድነት ሊሰራ እንደሚገባ ጠቁመው፤ ለዚህም ጉባዔው የበኩሉን ጥረት እንዲያደርግ አሳስበዋል።

በምልዓተ ጉባዔው ላይ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት የመጡ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የተገኙ ሲሆን በቤተክርስቲያኗ እና በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።

በዙፋን ካሳሁን

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!