የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ባንኮችን ለማጠናከር መስራት ይገባል

By Adimasu Aragawu

October 26, 2025

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 20 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፈርስት አዲስ ኢንቨስትመንት የተሰኘ ኢንዲፔንደንት የኢንቨስትመንት ባንክ በይፋ ሥራ ጀምሯል፡፡

በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ዘርፍ መሰማራት ለሚፈልጉ የሀገር ውስጥ እና ውጭ ተቋማት ፈቃድ መስጠት መጀመሩ ይታወቃል፡፡ይህን ተከትሎም ኢትዮጵያዊያን እና የውጭ ኩባንያዎች በኢንቨስትመንት ባንክ በመሰማራት ላይ እንደሚገኙ  የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣ አመልክቷል፡፡

በዚህ መሰረትም ፈርስት አዲስ ኢንቨስትመንት በ28 ሚሊየን ብር መነሻ ካፒታል ጥቅምት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ፈቃድ አግኝቶ ሥራ መጀመሩን ገልጿል፡፡

ተቋሙ በባንኮች እየተቋቋሙ ከሚገኙ ኢንቨስትመንት ባንኮች ውጪ ፈቃድ የተሰጠው የመጀመሪያ ገለልተኛ የኢንቨትመንት ባንክ በመሆን ነው ሥራውን የጀመረው፡፡

ፈርስት አዲስ ኢንቨስትመንት ባንክ ፍላጎት ተኮር የሆኑ የኢንቨስትመንት መፍትሄዎችን ለግለሰቦች፣ ለድርጅቶች እና ለመንግስት በማቅረብ የካፒታል ተደራሽነትን ማጎልበት እና ዘላቂ የኢኮኖሚ ልማትን ለማምጣት ይሰራል፡፡

ባንኩ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ለገበያ እንደ አዲስ በሚወጡበት ወቅት የማማከርና የማሳለጥ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን ÷ የተቋማትን ውሕደት እና ግዢ ማማከር ላም እንደሚሰራም ተጠቁሟል፡፡

ከዚህ ባለፈም የኢንቨስትመንት እና የኩባንያ ጥናትን እንዲሁም የኩባንያ እና የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ግመታን በመስራት አዲስ ካፒታል ማፈላለግ እና ማማከር ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ተመላክቷል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!