የሀገር ውስጥ ዜና

በአፋር ክልል በጎርፍ ውሃ የተከበቡ ወገኖችን በሄሊኮፕተር የማውጣቱ ስራ መጠናቀቁ ተገለፀ

By Tibebu Kebede

August 18, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 12 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአፋር ክልል በጎርፍ ተከበው የነበሩ ወገኖችን በሄሊኮፕተር ታግዞ የማውጣቱ ስራ መጠናቀቁን የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

የመከላከያ እና አየር ኃይል አባላት ላበረከቱት አስተዋጽኦ የክልሉ መንግስትና ህዝብ ከፍተኛ ምስጋናና አክብሮት እንዳላቸውም ተገልጿል።