ስፓርት

ሀዋሳ ከተማ ወላይታ ድቻን አሸነፈ

By abel neway

October 29, 2025

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ3ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሀዋሳ ከተማ ወላይታ ድቻን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡

ቀን 9 ሰዓት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሁለቱንም የሀዋሳ ከተማ የማሸነፊያ ግቦች ያሬድ ብሩክ አስቆጥሯል፡፡

ወላይታ ድቻን ከመሸነፍ ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ደግሞ ካርሎስ ዳምጠው ከመረብ አሳርፏል፡፡