ስፓርት

በቻይና በተካሄደው የማራቶን ውደድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች አሸነፉ

By Adimasu Aragawu

November 02, 2025

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በቻይና በቤጂንግ እና ሆንዙ በተካሄደው የማራቶን ውድድር በሁለቱም ፆታዎች ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች አሸንፈዋል።

በሆንዙ የማራቶን ውድድር በሴቶች አትሌት ሩቲ አጋ በ2:24:29 በሆነ ሰዓት በመግባት ውድድሩን አሸንፋለች።

በወንዶች አትሌት ጫሉ ደሶ በ2:11:15 በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቋል።

በተመሳሳይ በቤጂንግ በተካሄደው የማራቶን ውድድር በወንዶች አትሌት ለሚ ብርሃኑ 2:08:10 በመግባት ሲያሸንፍ÷ አትሌት ደሳለኝ ግርማ ሁለተኛ ወጥቷል።

በሴቶች አትሌት አንቻሉ ደሴ በ2:26:06 በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት ስታጠናቅቅ÷ ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ቁፍቱ ጣሂር ሦስተኛ ወጥታለች።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!