አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የደብረታቦር /ቡሄ/ በዓል ህዝባዊ ባህሉን፣ የቀደመ የአከባበር ታሪኩን በጠበቀ እና በተለየ መልኩ በደብረታቦር ከተማ እንዲከበር በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ።
በነገው እለት የሚከበረውን የደብረታቦር /ቡሄ/ በዓል አስመልክቶ የደብረታቦር ዩኒቨርሲቱ ፕሬዚዳንት ዶክተር አነጋግረኝ ጋሻው በሰጡት መግለጫ፥ በዓሉ “ደብረ ታቦርን በደብረ ታቦር” በሚል ስያሜ በከተማዋ በተለየ መልኩ ይከበራል ብለዋል።