ስፓርት

ፌዴሬሽኑ የአፍሪካ ባህል ስፖርቶች ኮንፌዴሬሽን አባልነት ማረጋገጫ ተሰጠው

By Adimasu Aragawu

November 06, 2025

‎አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን አባል የሆነበትን የአፍሪካ ባህል ስፖርቶች ኮንፌዴሬሽን የአባልነት ማረጋገጫ ሰርቲፊኬት በዛሬው ዕለት ተሰጠው። ‎ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ህይወት መሃመድ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ÷ ጥያቄው አስቀድሞ ተቀባይነት ማግኘቱን ጠቅሰው÷ በዚምባብዌ ሃራሬ ከተማ በተካሄደው ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ የማረጋገጫ ሰርቲፊኬት መረከባቸውን ተናግረዋል። ‎ ‎አባልነቱ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር ድንበር ተሻጋሪ የሆነ ግንኙነቶችን በመፍጠር ባህላዊ ስፖርቶቻችንን ለማስተዋወቅ ይረዳል ብለዋል። ‎ ‎በ1977 ዓ.ም የተመሰረተው የኢትዮጵያ ባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን የኢትዮጵያዊያን ባህላዊ ስፖርቶችና ጨዋታዎች በጥናትና ምርመር በመለየት ይዘታቸውን ጠብቀው ለትውልድ እንዲተላለፉ የማስተዋወቅ ስራዎችን እየሠራ ይገኛል። ‎ በሙባረክ ፋንታው

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!