ስፓርት

ሀዋሳ ከተማና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አቻ ተለያዩ

By abel neway

November 09, 2025

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ5ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሀዋሳ ከተማና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የሀዋሳ ከተማን ግብ ያሬድ ብሩክ አስቆጥሯል፡፡

አዲስ ግደይ ደግሞ የንግድ ባንክን የአቻነት ግብ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት ሸገር ከተማና ሀድያ ሆሳዕና ያደረጉት ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡