አዲስ አበባ፣ ሕዳር 2 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) አስከሬን ሽኝት ሥነ ሥርዓት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 6 ኪሎ ካምፓስ እየተካሄደ ነው፡፡
በሽኝት ሥነ ሥርዓቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች የሥራ ባልደረቦችና ወዳጅ ዘመዶች ተገኝተዋል።
የላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ሥርዓተ ቀብርም ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር ይፈጸማል፡፡
የታሪክ ተመራማሪው ላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ባደረባቸው ሕመም ሕክምናቸውን ሲከታተሉ ቆይተው ጥቅምት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ይታወቃል፡፡
ላጲሶ (ፕ/ር) በኢትዮጵያ እንዲሁም በአፍሪካ የታሪክ ጥናትና ምርምር በማካሄድ የተለያዩ የታሪክ መጻሕፍትን ለአንባቢያን አበርክተዋል፡፡
የኢትዮጵያውያንን የጋራ እሴት፣ ባሕልና ቋንቋ በማውሳት የሕዝቦች ታሪክ ጎልቶ እንዲታወቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውም ተጠቁሟል፡፡