ስፓርት

ከ17 ዓመት በታች የሴካፋ ዋንጫ በፋና+ ‎

By Adimasu Aragawu

November 18, 2025

‎የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ዋንጫ (ሴካፋ) ማጣሪያ ሁለተኛ የምድብ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን የሚያደርጉት ጨዋታ በፋና+ ቴሌቪዥን ቻናል በቀጥታ ይተላለፋል። ‎ ከ17 ዓመት በታች አፍሪካ ዋንጫ የሴካፋ ማጣሪያ ውድድር የሁለተኛ ቀን ጨዋታዎች በአበበ ቢቂላ እና ድሬዳዋ ስታዲየም ይደረጋሉ፡፡

የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ከደቡብ ሱዳን ዛሬ ከቀኑ 7 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም የሚያደርጉትን ጨዋታ ከፋና+ ቴሌቪዥን በተጨማሪ በፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ፌስቡክ እና ዩቱዩብ ገፆች በቀጥታ የምናስተላልፍ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ሩዋንዳን 2 ለ 0 ማሸነፉ ይታወሳል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!