የሀገር ውስጥ ዜና

ዶ/ር አንዷለም ዳኘ ላይ የግድያ ወንጀል የፈጸመው ተከሳሽ በ25 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣ

By Melaku Gedif

November 21, 2025

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የባሕር ዳርና አካባቢው ከፍተኛ ፍ/ቤት የጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሐኪም በነበሩት ዶ/ር አንዷለም ዳኘ ላይ የግድያ ወንጀል በፈፀመው ተከሳሽ ላይ የ25 ዓመት ጽኑ እስራት ወስኗል።

ፍ/ቤቱ ዛሬ በዋለው ችሎት በዶክተር አንዷለም ዳኘ የግድያ ጉዳይ ላይ የቀረበውን መረጃ እና ማስረጃ መሰረት አድርጎ ውሳኔ አሳልፏል።

በዶክተሩ ላይ ግድያው የተፈፀመው ጥር 24 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት ላይ ባሕር ዳር ከተማ የግል መኪናቸውን በሚያሽከረክሩበት ወቅት ጠብቆና ተዘጋጅቶ በጥይት ተኩሶ መግደሉን ፍርድ ቤቱ በቀረበ ማስረጃ አረጋግጧል።

በዚሁ ዕለት ምሽት ላይ በተመሳሳይ በሌላ የሕክምና ዶክተር ላይ ጥይት በመተኮስ የመኪናውን አካል በመምታት የግድያ ወንጀል ሙከራ ስለመደረጉም ፍርድ ቤቱ አመልክቷል።

የግድያ ወንጀሉ ከተፈጸመ ጊዜ ጀምሮ መረጃና ማስረጃዎችን በማሰባሰብ የተጠናከረ የምርመራ ቡድን ተቋቁሞ ሥራው ተጠናቅቆ ለፍርድ ቤቱ ቀርቧል።

በዚህ የምርመራ ሒደት ከክልሉ ፖሊስ ዋና መምሪያ እና ከከተማ አስተዳደሩ የምርመራ ቡድን ተዋቅሮ መረጃና ማስረጃዎችን በማሰባሰብ የወንጀሉን አፈፃፀምና ፈጻሚውን ማወቅ እንደተቻለ መጠቀሱን ኢዜአ ነው የዘገበው፡፡

ፍርድ ቤቱም የቀረቡለትን የምርመራ ውጤቶች መሰረት በማድረግ በዛሬው ዕለት በዋለው ችሎት ወንጀሉን በፈጸመው ግለሰብ እሱባለው ነበረ ላይ የ25 ዓመት ጽኑ እስራት ወስኖበታል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!