የሀገር ውስጥ ዜና

ኮርፖሬሽኑ ለሚያስገነባው የቢሾፍቱ ባቡር አካዳሚ መሰረት ድንጋይ ተቀመጠ

By Adimasu Aragawu

November 22, 2025

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ለሚያስገነባው የቢሾፍቱ ባቡር አካዳሚ መሰረት ድንጋይ ተቀመጠ።

በመርሐ ግብሩ ላይ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ህሊና በላቸውን (ኢ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ ሚኒስቴሩ በባቡር መሰረተ ልማት ክልሎችን በማስተሳሰር የሀገሪቱን የሎጂስቲክስ ፍላጎት ለማሳለጥ እየሰራ ይገኛል።

በዛሬው ዕለት መሰረት ድንጋይ የተቀመጠለት የባቡር አካዳሚ ከውጭ የሚገቡ ባለሙያዎችን በመቀነስ ኢትዮጵያ በቀጣናው ማዕከል እንድትሆን ያደርጋታል ብለዋል።

ይህም ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች በዓለም ገበያ ውስጥ የስራ ዕድል እንዲያገኙ ከማስቻል ባለፈ ለኢትዮጵያም የውጭ ምንዛሪ ማግኛ እንደሚሆን አመላክተዋል።

ህሊና በላቸው (ኢ/ር) በበኩላቸው የአፍሪካን የባቡር ትራንስፖርት በዕውቀት ለመደገፍ ማዕከሉ አስተዋፅኦ እንዳለው አንስተው÷ አካዳሚው ለትውልድ ትምህርት ቤት ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያ ብልፅግና መሰረት ነው ብለዋል።

የቢሾፍቱ ከተማ ከንቲባ አለማየሁ አሰፋ የአካዳሚው መገንባት የቱሪስት መዳረሻ ለሆነችው ቢሾፍቱ ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥር ተናግረዋል።

በፍቅርተ ከበደ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡- YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Facebook https://web.facebook.com/fanasport Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!