የሀገር ውስጥ ዜና

የሃገሪቱን ደህንነት አደጋ ላይ በመጣል የመንግስትን የደህንነት ሚስጥር በውጭ ላለ የሽብር ቡድን አሳልፈው በመስጠት የተጠረጠሩ ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀረቡ

By Tibebu Kebede

August 19, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 13 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ህውሃት ፅህፈት ቤት የቀድሞ ሃላፊ አቶ ተወልደ ገብረጻዲቅ፣ የህግና ፍትህ ዳይሬክተር አቶ ተስፋለም ይደጉ እና የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የደህንነት ሃላፊ አቶ አጽብሃ አለማየሁን ጨምሮ አምስት ተጠርጣሪዎች ዛሬ በከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀረቡ።

ተጠርጣሪዎቹ ከዚህ በፊት በመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሃገሪቱን ደህንነት አደጋ ላይ በመጣል የመንግስትን የደህንነት ሚስጥር በውጭ ላለ የሽብር ቡድን አሳልፈው ሰጥተዋል ተብለው ምርመራ ሲደረግባቸው የነበሩ ናቸው፡፡